02/07/2016
ለተመራቂ ተማሪዎችና ቤተሰቦች እንኳን ደስ አላችሁ
ወደ ጣና ፈርጧ ባህር ዳር ሲመጡ ከኩሪፍቱ ፊት ለፊት የሚገኘው የውዴ ቡና ቁርስ ጨጨብሳው የተጨበጨበለት ነው ቡናውም እንደዛው:: የጀበና ቡና ሲፈልጉ በፔዳ መስመር 'አዜብ ቡና' ከራንዲቡ ፊት ለፊት፤ ቀበሌ 14 'አኮቴት 'ባርና ሬስቶራንት፤ጣና ሐይቅ ዳርቻ የፎቶ አንሽዎች ማህበር 'ኮከል"፤ከታደሰ ፔንሲዬን ጎን 'ቤቲ ቡና'፤መብራት ሐይል ህንፃ 'ኒውላይት' ባርናሬስቶራንት ውስጥ የፈረስ ጭራ የመሰለ የጀበና ቡና ያገኛሉ:: እንግዳ በመቀበልና በመሸኘት ወደር የማይገኝላቸው የባጃጅ ሹፌሮች ከአሉበት ቦታ እስከፈለጉት ቦታ ድረስ ከ15-20 ብር ድረስ በኮንትራት አገልግሎት ለመስጠት ዝግጁ ናቸው::አሳ ጥብስ ካማርዎት ጣና ሀይቅ ትራንስፖርት ውስጥ ፤ሆስፒታል መንገድ ሀይሌ ፔንሲዮን፤ሜላት ካፌ ጎን ያጀብ አበረ ሬስቶራንት፤ከግሩም ጋይንት ፔንሲዮን ፊት ለፊት ፍቅር አሳ ቤት ያገኛሉ:: የሙስሊም ምግብ ቤቶች ከሚሊኒየሞ ካፌ አጠገብ ማሻ አላህ ፤ብርሃን ባንክ አጠገብ ሰላም ሻይ ቤት ውስጥ::የጣናን ንፋስ ለመኮምኮም በዙሪያው የከበቡትን የሆቴል አገልግሎት የሚሰጡትን ልንገርዎት ብሉናይል ሪዞርት፤ደሴት ሎጅ፤ግራንድ ሆቴልና ስፓ፤ኩሪፍቱ ሪዞርት፤ጣይቱ መዝናኛ ማዕከል፤ሌክሹር ባርና ሬስቶራንት፤ካስትል ኩሪፍቱ ወይን ሐውስ፤ሙንላይት ካፌና ሬስቶራንት፤ ጣና ሆቴል ሲሆኑ ህዳር11 መናፈሻ ምንም አይነት ወጭ ሳያወጡ ጣናን እያዬ የሚናፈሱበት ቦታ ነው አንዳንዶቹ 'የደሃ መዝናኛ' ይሉታል::አሁን ጣናን ሲያዬ መዋኘት ካሰኘዎት ወደ ኤርፖርት መንገድ አየር ሀይል መናፈሻ ውስጥ የተንጣለለ ንፁህ መዋኛ ገንዳ አለ፣መሀል ከተማ ፓፒረስ ሆቴል ፤ከባህርዳር ዩንቨርቲ ፖሊ ፊት ለፊት ሹም አቦ መናፈሻ ፤ባ/ዳር ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ፤በቅርብ የሚጀምረው የአረጋውያን ማህበር ህንፃ ላይ መዋኘት ይችላሉ:: በጣና ሀይቅ ዙሪያ ያሉ ገዳማትንና ደሴቶችን ለመጎብኘት የባህርዳር የጀልባ ኪራይና አስጎብኝዎች ማህበር በደንብ ያስተናግዳሉ:: የጣናን ዳርን በእግር ለመጓዝ ከፈለጉ በህዳር 11 ገብተው እስከ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ከመጡ በሗላ እንደገና በበርኖስ አርት ጋላሪ ይገቡና እስከ ጣናሆቴል ድረስ ይጓዛሉ::ይህን ጉዞ ወደምሽቱ 11:30 አካባቢ ቢያደርጉት ፀሐይ ወደ ሌላ ሀገር ስትሄድ ሲመለከቱ ሀሴት ያደርጋሉ::
ምሳ ሰዓት ወደ ሌክሹር ባርና ሬስቶራንት ጎራ ቢሉ የሌክሹር ስፔሻል ምግብ እጅያስቆረጥማል፤ከኢትዮ ስታር ጀርባ 'ሌማት 'በተባለው ሬስቶራንት" ባናቱ "የተሰኘው ምግባቸው በጣዕሙ ብቻ ሳይሆን ብቻዎትን አይጨርሱትም፤አዲስ አምባ ሆቴል ፒዛቸው ከነሙሉ መስተንግዶው ውጡ ውጡ አያሰኝም፤ ነፍሰጥሮች የአዘዋ ጥብስ አማረኝ ይላሉ ከብሔራዊ ስታድየም መግቢያ ላይ ይገኛል ጎራ ማለት ነው፤በተለምዶ ትራፊክ መብራቱ በሚባለዉ አካባቢ ፒያሳ(ዬም ሆቴሎች ) ክሽን ያለ የበግ ጥብስ ምሳና እራት አይጠፋም፤ ሽሮ በቲማቲም በእምነትና ሩሃማ የተሰኙ ከኢትዬ ስታር ጀርባ እንዲሁም ከማዘጋጃ (ከተማ አገልግሎት) ፊት ለፊት ዝናሽ ሽሮ ጮማ ለምኔ የሚይስብሉ ሽሮ ቤቶች ናቸው፤ዲፖ አካባቢ ላይ 'ምስራቅ' ሬስቶራንት ውስጥ ከዚህ በፊት በልተውት የማያውቁት የምግብ አይነቶች ያገኛሉ ልክ እንደአዲስ አበባው ጫኔ ሬስቶራንት በተለይ ምስራቅ የተሰኘው በየአይነት አሪፍ ነው:: ብቻ ባ/ዳር ላይ በ10 ብር ቆንጆ ሽሮ ከመናህሪያው ጀርባ ያሉት ኮንቴነሮች ላይ ያገኛሉ የምግብ እርካሽ ባ/ዳርን የሚዳደራት አይገኝም:: ከምሳ በሗላ መሀል ከተማ የሚገኘው ሀይፐር ሲኒማ ወይም ወደ አዲስ አበባ መውጫ የተባበሩት ነዳጅ ማደያ ፊትለፊት የሚገኘው ባህርዳር ሲኒማ አዳዲስ የአማረኛ ፊልሞች ማየት ይችላሉ::
ፀጥታ የሰፈነበት መናፈሻ አባይ ምንጭ ሎጅ ተመራጭ ነው:: ለጫጉላ ሽርሽር ጢስ አባይ አይቀርም :: ግዙፉ ስታድየምና ሰማዕታት ሀውልት ይጎበኛሉ::
የደለበ ሰንጋ ስጋ ከሚያገኙበት መካከል ሆስፒታል መስመር እምነት ስጋ ቤት፤ ገጠር መንገድ ሳሚ ቁርጥ ቤት፤ባለእግዛብሔር ቤተክርስቲያን አካባቢ ማኛ ቁርጥ ቤት፤ የተባበሩት አሜንዳ ቁርጥ ቤት የስጋ አምሮትዎን ከጃንቦ ድራፍት ጋር ያወራርዳሉ:: ወደቤዛዊት ተራራ በመሄድ የባህርዳርን ሙሉ ገፅታ በርቀት ያያሉ ::እዚህ ላይ ባህርዳር ብቻ የሚጠመቀውን ከባ/ ዳር ዬንቨርስቲ ቢሮ ህንፃ ከጨገብ የሚገኘውን የፔልካን ምርት የሆነውን ወይን ቢጎነጬበት አሪፍ ትዝታ አለው::ከተራራው ሲመለሱ አባይ ማዶ የሚገኘው ኮብል መናፈሻ ከገቡ የሴራል ድራፍት ያገኛሉ:: አሁን እየመሸ ነው ማሲንቆና ከበሮ ቤቶች ውሰጥ ከዘለሰኛ አሰከ ጎጃም እንቅጥቅጥና ፉከራ ከሽለላ ጋር ለማየት ጎራ ይበሉ ::ቱባ የሆነውን የአዝማሪ ግጥም አወራረድ የጎጃም፣የጎንደር፣የሰቆጣ፣የአዊና የሌሎች ብሔር ጭፈራ ለማየት
ባላገሩ፣ወንድማማቾች፣አዋሽ፣አልማዝ፣ፈንድቃ የተሰኙ ቤቶች ተዝናኑ::ባህል ዘመናዊ ሁነው በባንድ ከሚታጀቡት ውስጥ አምሳል ምትኬ ከሙሉአለም የባህል ማዕከል ፊት ለፊት፤ጨጨሆ ከኩሪፍቱ ፊት ለፊት፤ ጃሎ በል ሙሉአለም የባህል ማእከል ግቢ ውስጥ ፤ካስትል ኩሪፍቱ ወይን ሀውስ ከፖሊ ፊት ለፊት የሚገኙ ሲሆን አርብ አርብ በጃማይካዎች የሚታጀብ ሬጌ ናይት በኤንጅጅ ሆቴልና ሬስቶራንት ይቀርባል:: ከጭፈራ ቤቶች መካከል ሲቲ ባር፣ ጆን ባር፣ጀሪ ባር፣ኤክሶዶስባር፣ሊሊታ ባር፣ማሪንጌቻ ባር፣ኦፊስ ባር ዘና ማለት ይችላሉ:: ምሽት ላይ የተቀቀለ ድንችና እንቁላል በየጭፈራ ቤቱ በር ላይ አያጡም ነገር ግን ክቡር የተሰኘ ሬስቶራንት 24 ሰዓት ክፍት ነው
አንግዲህ ባህርዳርን የጉብኝት ግዜዎትን ሲጨርሱ የስጦታ መሸጫ ቦታዎችን እንጠቁምዎ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን መግቢያ ላይ ያሉ ኮንቴነሮች፤ፓፒረስ ሆቴል በር ላይ፤ድብ አንበሳ ሆቴል ፊት ለፊት፤ ከፖስታ ቤት አጠገብ ፤ሰርፀ ድንግል ት/ቤት መግቢያ ላይ ሲኖሩ የባህርዳር መገለጫ የሆኑ እነ አገልግል፣የእንጀራ ሞሰብ፣በቆዳ የተሰሩ ኩርሲዎች፣ሸበጥ ጫማዎች ፣አንባር፣አልቦ፣ጠልሰሞች ከፓፒረስ ሆቴል ጀርባ ያሉ ኮንቴነሮች በተመጣጣኝ ዋጋ ያገኛሉ::
ባህርዳር ያፈራቻቸው የእውቅ ሰዓሊያን እያዬ ገነት፣ሀይሌ ዘውዱ፣በረከት አንዳርጌ ናሙሉጌታ በላይ በየጋላሪያቸው በተመጣጣኝ ዋጋ ምርጥ ምርጥ ስዕሎች ይቸበቸባሉ::
ደምስ አያሌው ቢሻው
ሰኔ 24/2008 ዓ.ም