06/08/2024
ቀን 29/11/2016 ዓ.ም
ለውድ ደንበኞቻችን፣
==ዉበት ሆቴልን በተመለከተ ሰሞኑ በሶሻል ሚዲያ
(Face book) ላይ የተለጠፈው ጉዳይን ይመለከታል፤==
ሆቴላችን በመንግስታዊ ጫና/ተፅዕኖ ምክንያት ሙሉ በሙለ እንደተዘጋ ተደርጎ በተለያዬ Face book ጌጽ ላይ እንደተፖሰተ/እንደተፃፈ የተመለከቱ በቁጥር በረካታ ደንበኞቻችንና አጋሮቻችን በስልክ ስለጉዳዩ ጠይቃችኋናል፡፡ ለዚህም ለእናንተ ያለን ታላቅ አክብሮታችን በዚህ አጋጣሚ እየገለጽን፤ ጉዳዩን በተመለከተ እውኔታውን እንደሚከተለው ለማሳወቅ ወደድን፡፡
ከላይ እንደተገለፀው ሆቴላችን በተመለከተ በማህበራዊ ድህረ-ገፅ (Face book ) የተሰረጨውን ወረ ከደንበኞቻችን በስልክ በደረሰን ጥቆማ መሠረት በማህበራዊ ድህረ-ገፅ ላይ ማየት ችለናል፡፡ ሆቴላችን ለውድ ደንበኞቻችን ደረጃውን በጠበቀ እና አሁን ካለበት ደረጃ በተሻለ ሁኔታ የሆቴል አገልግሎት ለመስጠት በማስብ እና ለዚህም ቅድመ ዝግጅት ለማድረግ ያስችለን ዘንድ ከሐምሌ ወር 2016 ዓ.ም ጀምሮ ቀደሞ ሲስጥ የነበረው አገልግሎት በማቆም የእድሳት ሥራ ጀምረናል፡፡ ነገር ግን እውኔታው ይህ ሆነው ሳለ እኛ በማናውቅበት መንገድ ፤ የተለያየ የአሉባልታ እና የሐሴት መረጃዎች በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ተሰራጭቷል፡፡ ሆቴላችን ሥራ ከጀመረበት ጊዜ አንስተው እስከ ዛሬ ድረስ በየትኛውም አጋጣሚና ሁኔታ፤ ከየትኛውም አካል የደረሰብና አሉታዊ ጫናዎች እና ችግሮች ቢኖሩ እንኳን ፤ በተገቢ ሁኔታ ለሚመለከተው አካል በማሰውቅ/ጥያቄ በማቅረብ ተገቢ ምላሽ እያገኘን ቆይተናል፡፡ እንዲሁም ተገቢ ምላሽ ያላገኘንባቸው ጉዳዮች ቢኖሩ እንኳን በስሜት ተነሳስተን በእንደዚህ (በሶሻል ሚዲያ እየተባለ እንዳለው) ሁኔታ/ መንገድ መልስ ይገኛል ብለን አናምንም!
ስለሆነም ሆቴላችን በተመለከተ በማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጨው ነገር ውሸት መሆኑን እና ሆቴሉን የማይመለከት መሆኑን እየገለጽን፤ ይህን አሉባልታ በሶሻል ሚዲያ ያጋሩ አካላት (ማንነታቸው የሚታወቅና የማይታወቁ) መረጃውን ከማን አግኘተው ወይም ምን አነሳስቷቸው እንደሆነ ከሚመለከተው አካል ጋር በመሆን እያጣራን እንገኛለን፡፡
ውጤቱን እና እውኔታውን በቅርብ አብረን የሚናየው ይሆናል!
ከሠላምታ ጋር!